መልካም የሆነ ማኀበራዊ ትስስር
በመተባበር ላይ የተመሠረተ መተዛዘንና የሰፈነበት ሕዝባዊ ትስስር መፍጠር የደስታን መንፈስ ስቦ የማምጣት አቅም አለው
እንዲህ ዓይነት የሲቨል ተቋማት በኢስላም ወርቃማ ዘመን ብልጭ ብለው ከጠፋ ወዲህ በየትም ሀገርና
በየትኛውም ሥርዓት ደግም ለመከሰት አልበቁም ጠንካራ የሙስሊሞች ማኅበረሰብ የጠንካራ እምነት ፍሬ እንጂ ሌላ ምን ሊሰኝ ይችላል!?
... ያ ትውልድ በርግጥ ፈጣሪው በነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በኩል መልዕክት ላከለት እርሱም ያለማቅማማት ወዶ ተቀበለ::
በዚህም የሥልጣኔ ቁንጮ ሆኖ በታሪክ ዓምዶች ላይ አንፈራጠጠ፤ የዚህ ሁሉ የመጨረሻ ውጤት ደስታና ብልፅግና መሆኑ እዚህ ላይ ሊሰመርበት ይገባል::
ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)
<<የአማኞች ሁኔታ ሕንፃውን እንደተሠራበት ጡብ ነው አንዱ ሌላውን በመደገፍ ሕንፃውን ያቆሙታል>> (ኢማሙ ቡኻሪና ሙስሊም)
<<የምመእናን እርስ በርስ መደጋገፍና መተዛዘን አምሳያው እንደ አንድ አካል ነው
ከአካላችን ውስጥ አንዱ ጣታችን ቢታመም መላው ሰውነታችንም አብሮ ይታመማልና>> (ቡኻሪና ሙስሊም)
<<ከናንተ አንዳችሁ ለራሱ የሚወደውን ነገር ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ አላመነም>> (ቡኻሪና ሙስሊም)
አንድ መስሊም በሌላ ሙስሊም ወንድሙ ላይ የሚከተሉት ግዴታዎች ይፀኑበታል
1. ስትገናኙ ስላምታን መለዋወጥ (ይኸውም የአላህ ስላም ባንተ ላይ ይሁን የሚለውን ነው)
2. ቢጋብዝህ ግብዣውን መቀበል
3. ምክር እንድትለግሰው ቢጠይቅህ በሐቅ ላይ ሆነህ ከልብህ ምከረው
4. ቢያስነጥሰውና አላህን ቢያመሰግን አላህ ይዘንልህ (ይማርህ) በማለት ዱዓ አድርግለት
5. ሲታመም ጠይቀው
6. ሲሞት አስክሬኑን ሽኝ (ቅበረው) (ኢማም ሙስሊም)
<<በአላህ በፍርዱ ቀን ያመነ ሰው በጎረቤቱ ላይ መጥፎ ድርጊት አይፈጽም
በአላህ ና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር
በአላህ በፍርዱ ቀን ያመነ በጎ ነገር ይናገር ወይም ዝም ይበል>> (ቡኻሪና ሙስሊም)
በማለት እንደ ማር ጠብታ የሚጣፍጥ ምክራቸውን አንቆርቁረውልናል::
ሁለተኛው የኢስላም ኸሊፋ ዑመር ቢን አል-ኸጧብ (ረ.ዐ) ለሁሉም
ሰው በበቂ ሁኔታ እስኪዳረስ ድረስ ቅባት ያለው ነገርና ሥጋ ላለመመገብ ወስነው ነበር::
እንዲህ ያለው በሥነ-ምግባር አንፃር በዓለም ላይ ከታዩ ህዝቦች ሁሉ ቁንጮ የሆነ ማኀበረሰብ አንዱ ለሌላው ወንድሙ ሲል የራሱን ጥቅም አሳልፎ በመስጠት በመዋደድና በመላላቅ የደስታን ባሕር በቁጥጥሩ ሥር አድርጎ እንደፈለገ ሲቀዝፍና ሲዋኝበት መኖሩ አያስደንቅም!?
በመተባበር ላይ የተመሠረተ መተዛዘንና የሰፈነበት ሕዝባዊ ትስስር መፍጠር የደስታን መንፈስ ስቦ የማምጣት አቅም አለው
እንዲህ ዓይነት የሲቨል ተቋማት በኢስላም ወርቃማ ዘመን ብልጭ ብለው ከጠፋ ወዲህ በየትም ሀገርና
በየትኛውም ሥርዓት ደግም ለመከሰት አልበቁም ጠንካራ የሙስሊሞች ማኅበረሰብ የጠንካራ እምነት ፍሬ እንጂ ሌላ ምን ሊሰኝ ይችላል!?
... ያ ትውልድ በርግጥ ፈጣሪው በነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በኩል መልዕክት ላከለት እርሱም ያለማቅማማት ወዶ ተቀበለ::
በዚህም የሥልጣኔ ቁንጮ ሆኖ በታሪክ ዓምዶች ላይ አንፈራጠጠ፤ የዚህ ሁሉ የመጨረሻ ውጤት ደስታና ብልፅግና መሆኑ እዚህ ላይ ሊሰመርበት ይገባል::
ነብዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)
<<የአማኞች ሁኔታ ሕንፃውን እንደተሠራበት ጡብ ነው አንዱ ሌላውን በመደገፍ ሕንፃውን ያቆሙታል>> (ኢማሙ ቡኻሪና ሙስሊም)
<<የምመእናን እርስ በርስ መደጋገፍና መተዛዘን አምሳያው እንደ አንድ አካል ነው
ከአካላችን ውስጥ አንዱ ጣታችን ቢታመም መላው ሰውነታችንም አብሮ ይታመማልና>> (ቡኻሪና ሙስሊም)
<<ከናንተ አንዳችሁ ለራሱ የሚወደውን ነገር ለወንድሙ እስካልወደደ ድረስ አላመነም>> (ቡኻሪና ሙስሊም)
አንድ መስሊም በሌላ ሙስሊም ወንድሙ ላይ የሚከተሉት ግዴታዎች ይፀኑበታል
1. ስትገናኙ ስላምታን መለዋወጥ (ይኸውም የአላህ ስላም ባንተ ላይ ይሁን የሚለውን ነው)
2. ቢጋብዝህ ግብዣውን መቀበል
3. ምክር እንድትለግሰው ቢጠይቅህ በሐቅ ላይ ሆነህ ከልብህ ምከረው
4. ቢያስነጥሰውና አላህን ቢያመሰግን አላህ ይዘንልህ (ይማርህ) በማለት ዱዓ አድርግለት
5. ሲታመም ጠይቀው
6. ሲሞት አስክሬኑን ሽኝ (ቅበረው) (ኢማም ሙስሊም)
<<በአላህ በፍርዱ ቀን ያመነ ሰው በጎረቤቱ ላይ መጥፎ ድርጊት አይፈጽም
በአላህ ና በመጨረሻው ቀን ያመነ እንግዳውን ያክብር
በአላህ በፍርዱ ቀን ያመነ በጎ ነገር ይናገር ወይም ዝም ይበል>> (ቡኻሪና ሙስሊም)
በማለት እንደ ማር ጠብታ የሚጣፍጥ ምክራቸውን አንቆርቁረውልናል::
ሁለተኛው የኢስላም ኸሊፋ ዑመር ቢን አል-ኸጧብ (ረ.ዐ) ለሁሉም
ሰው በበቂ ሁኔታ እስኪዳረስ ድረስ ቅባት ያለው ነገርና ሥጋ ላለመመገብ ወስነው ነበር::
እንዲህ ያለው በሥነ-ምግባር አንፃር በዓለም ላይ ከታዩ ህዝቦች ሁሉ ቁንጮ የሆነ ማኀበረሰብ አንዱ ለሌላው ወንድሙ ሲል የራሱን ጥቅም አሳልፎ በመስጠት በመዋደድና በመላላቅ የደስታን ባሕር በቁጥጥሩ ሥር አድርጎ እንደፈለገ ሲቀዝፍና ሲዋኝበት መኖሩ አያስደንቅም!?