ሶስት ቁልፍ መልእክቶች
ቁልፍ 1: በቁርአን ውስጥ ስለ ረመዳን ጾም አህካሞች የተነገረበት ቦታ አንድና አንድ ብቻ ነው፥ እርሱም ሱረቱል በቀራ 185ኛው አንቀጽ:: ይሁንና ይህ አንቀጽ ሀተታውን የሚጀምረው ድሮ ጀምሮ የምናውቀውን አጀንዳ መልሶ በማውሳት ነው:: ይኸውም ቅዱስ ቁርአን ለሰው ልጆች ሁሉ መንገድ አመላካችና እውነትን ከሀሰት የሚለዩበት ደማቅ መመሪያ መሆኑን ነው:: ይህ ማለት ደግሞ ረመዳን በመጣ ቁጥር ከጾሙ እኩል ሊተገበር የሚፈለገው ጉዳይ ቁርአኑን እንደ አዲስ መተዋወቅና ለሌሎች ማስተዋወቅ ነው:: ረመዳን ማለት የምናውቃቸውን አያዎች ሳይቀር እንደአዲስ በግርምት የምንተዋወቅበት ልዩ አጋጣሚ ነው:: በተጨማሪም ሙስሊም ላልሆኑ ጎረቤቶች ከሳምቡሳና ሾርባ በላይ በስጦታ መልክ ልናበረክትላቸው የሚገባ ወደር የለሽ ሽልማትም ነው - ቅዱስ ቁርአን::
ቁልፍ 2: ስለ ረመዳን ወር ሁኔታ ዝርዝር ሀሳብ ከተደመጠ በኋላ ቀጥሎ የሰፈረው መልእክት ደግሞ ዱአን የሚመለከት ነው:: ይታይህ እንግዲህ፥ ስለ ጾም ሲወሳ የማይታለፍ ርእስ ቢኖር የጾመኛ ሰው ዱአ ነው:: ቀደምት ሷሊሆች ለወጥ ማጣፈጫ ጨው ያጡ ለታ እንኳ ጎረቤት ከመበደር ይልቅ እጃቸውን ማንሳት ይቀላቸው ነበር:: የገባንበት አስቸጋሪ ፈተና በሱጁዶች ውስጥ ከሚደረጉ ዱአዎች ጋር ሲነጻጸር የትንኝ ክብደት አያህልም:: የኡማው የዘወትር ድል የተጠራቀመውም እዚሁ ወር ላይ በሚሰሙ ዱአዎች ውስጥ ነውና በባዶ መጨነቃችንን ትተን ዱአችንን እንያያዘው::
ቁልፍ 3: ቀጣዩ አያ ደግሞ ስለ ቤተሰብ ጉዳይ ያነሳል:: ወንድና ሴት እርስ በእርስ የሚሸፋፈኑ ጥንዶች መሆናቸው በመጥቀስ ይህንን የድል ወር ወንዶች ከሴቶች ላይ ሴቶችም ከወንዶች ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ነውሮችን እንዲሁም የስራ ጫናዎችን መሸፋፈን፣ መከፋፈል እንዳለብን ይጠቁማል:: በረመዳን ውድ ግዚያቶች ላይ ሴቶች ቱርክ ፊልም ላይ የሚታዩ ምግቦችን የሚለማመዱበትና ወንዶች ደግሞ ቁርአንን ሺ ግዜ የሚደጋግሙበት ልማድ መታደስ አለበት:: ረመዳኑ የቁርአን፣ ረመዳኑ የዱአ፣ ረመዳኑ የለይል ሶላት እንጂ ረመዳኑ የ "ጣሽ መጣሽ" እና የምግብ ትምህርት ቤት እንዳይሆን ልዩ ትኩረት ይደረግ!
ቁልፍ 1: በቁርአን ውስጥ ስለ ረመዳን ጾም አህካሞች የተነገረበት ቦታ አንድና አንድ ብቻ ነው፥ እርሱም ሱረቱል በቀራ 185ኛው አንቀጽ:: ይሁንና ይህ አንቀጽ ሀተታውን የሚጀምረው ድሮ ጀምሮ የምናውቀውን አጀንዳ መልሶ በማውሳት ነው:: ይኸውም ቅዱስ ቁርአን ለሰው ልጆች ሁሉ መንገድ አመላካችና እውነትን ከሀሰት የሚለዩበት ደማቅ መመሪያ መሆኑን ነው:: ይህ ማለት ደግሞ ረመዳን በመጣ ቁጥር ከጾሙ እኩል ሊተገበር የሚፈለገው ጉዳይ ቁርአኑን እንደ አዲስ መተዋወቅና ለሌሎች ማስተዋወቅ ነው:: ረመዳን ማለት የምናውቃቸውን አያዎች ሳይቀር እንደአዲስ በግርምት የምንተዋወቅበት ልዩ አጋጣሚ ነው:: በተጨማሪም ሙስሊም ላልሆኑ ጎረቤቶች ከሳምቡሳና ሾርባ በላይ በስጦታ መልክ ልናበረክትላቸው የሚገባ ወደር የለሽ ሽልማትም ነው - ቅዱስ ቁርአን::
ቁልፍ 2: ስለ ረመዳን ወር ሁኔታ ዝርዝር ሀሳብ ከተደመጠ በኋላ ቀጥሎ የሰፈረው መልእክት ደግሞ ዱአን የሚመለከት ነው:: ይታይህ እንግዲህ፥ ስለ ጾም ሲወሳ የማይታለፍ ርእስ ቢኖር የጾመኛ ሰው ዱአ ነው:: ቀደምት ሷሊሆች ለወጥ ማጣፈጫ ጨው ያጡ ለታ እንኳ ጎረቤት ከመበደር ይልቅ እጃቸውን ማንሳት ይቀላቸው ነበር:: የገባንበት አስቸጋሪ ፈተና በሱጁዶች ውስጥ ከሚደረጉ ዱአዎች ጋር ሲነጻጸር የትንኝ ክብደት አያህልም:: የኡማው የዘወትር ድል የተጠራቀመውም እዚሁ ወር ላይ በሚሰሙ ዱአዎች ውስጥ ነውና በባዶ መጨነቃችንን ትተን ዱአችንን እንያያዘው::
ቁልፍ 3: ቀጣዩ አያ ደግሞ ስለ ቤተሰብ ጉዳይ ያነሳል:: ወንድና ሴት እርስ በእርስ የሚሸፋፈኑ ጥንዶች መሆናቸው በመጥቀስ ይህንን የድል ወር ወንዶች ከሴቶች ላይ ሴቶችም ከወንዶች ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ነውሮችን እንዲሁም የስራ ጫናዎችን መሸፋፈን፣ መከፋፈል እንዳለብን ይጠቁማል:: በረመዳን ውድ ግዚያቶች ላይ ሴቶች ቱርክ ፊልም ላይ የሚታዩ ምግቦችን የሚለማመዱበትና ወንዶች ደግሞ ቁርአንን ሺ ግዜ የሚደጋግሙበት ልማድ መታደስ አለበት:: ረመዳኑ የቁርአን፣ ረመዳኑ የዱአ፣ ረመዳኑ የለይል ሶላት እንጂ ረመዳኑ የ "ጣሽ መጣሽ" እና የምግብ ትምህርት ቤት እንዳይሆን ልዩ ትኩረት ይደረግ!